Saturday, May 5, 2012

የዋልድባ ገዳም ዝርፊያ ተፈፀመበት

የዋልድባ ገዳም በአምስት መሳሪያ ታጠቁ ፊታቸዉን የተሸፋፈኑ ግልሰቦች 66 ሺ ብር እንደተዘረፈ ምንጮች ጠቆሙ፡፡ ባለፈዉ ማክሰኞ ሌሊት ወደ ገዳሚ ገብዉ ዝርፊያ ፈፅሟል የተባሉት ግለሰቦች ወደ ቦታዉ ሲደርሱ ክላሽንኮቭ መሳሪያቸዉን በመጠቀም በገዳሙ የሚገኙትን መነኮሳት በአንድ ክፈል ከቆለፉ በሓላ ዝርፊያዉን እንዳከናወኑ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ ዘራፊዎቹ በቤተ እግዚያብሔር ዙሪያ የሚገኙትንና የተቆለፉትን ግማጃ ቤቶች፣ የነዋዬ ቅዱሳት ማስቀመጫ እቃ ቤትና የእህል ጎተራዎችን ሰብረዉ በመግባት 66ሺ ብር ከማስዳቸዉም በላይ ጥንታዊና ታሪካዊ ቅርሶችን በመበታተን በእቃዎቹ ላይ ጉዳት እንዳደረሱ ተገልፃል::   /አድስ አድማስ ጋዜጣ-ሚያዚያ 27-2004/



------------------------------------------------------------------------------- -------------------------------------------------------------------------------

No comments:

Post a Comment