Friday, May 4, 2012

ማራኪ ገጾች

ማንበብ ሙሉ ሰዉ ያደርጋል የሚል አንድ የቆዬ አባባል አለ። በርግጥም ማንበብ ሙሉ ሰዉ ብቻ ሳይሆን ሙሉ ሀገርና ሙሉ ተስፋ እንዲኖረን በማድረግ የተሻለ ትዉልድ እንዲፈጠር ያደርጋል። ነገር ግን ኢትዮጵያኖች ብሎም አፍሪካኖች የማንበብ ባህላችን ገና ያልዳበረና “አፍሪካዊያን እንዳያዉቁት የምትፈልገዉን ሚስጥር መጸሐፍ ዉስጥ ደብቀዉ” ተብሎ እስከሚሳለቅብን ድረስ ሗላ ቀር እንደሆነ ለማንም የተሰዎረ ሀቅ አይደለም። አንድ መጽሔት የአፍሪካ ምሑራን አንድ ጊዜ ዲግሪያቸውን ካገኙ በኋላ ስለማያነቡ ወደ መሐይምነት ይቀየራሉ በማለት ነበር የገለጻቸዉ፡፡ ነገር ግን ዲግሪ ለተወሰነ የትምህርት ዘርፍ የሚሰጠ ማስረጃ እንደመሆኑ መጠን፣ ምሑራንም ሆኑ ማንኛውም ሰው ማንበብ ይገባዋል፡፡ ይህም ተምሮ ከማያነብ ሰነፍ ይልቅ ባለመማሩ የማያነብ መሐይም የተሻለ ተስፋ አለዉና ነዉ። በመሆኑም የዚህ አምድ ዋና አላማ ከተለያዩ መጸሐፍቶች ገጽ  ላይ ሰዎችን ለተጨማሪ ንባብ ይኮረኩራሉ ያልናቸዉን ጥቂት አንቀጾችን (በመዉሰድ) በመዉሰድና ለንባብ በማቅረብ የተሻለ የማንበብ ባህል እንዲኖረን ለሚደረገዉ ጥረት የራሱን አስተዋጾ ማበርከት ነዉ።

------------------------------------------------------------------------------- -------------------------------------------------------------------------------

No comments:

Post a Comment