Thursday, August 30, 2012

ይህ እኮ የእኔ እንጂ የአንተ አገር አይደለም!

 
ፀሐፊ [ሞረሽ] ምድብ [ኑሮና ፖለቲካ]


በዚህ ልንጨርሰው ባገባደድነው አመት ጥቅምት ወር ውስጥ ለስራ ጉዳይ ከአዲስ አበባ ተነስቼ ወደ ሀገሪቱ ምዕራብ ክፍል መዳረሻየን ጋምቤላ ክልል ወደ ምትገኝ ዲማ ከምትባል ትንሽ የገጠር ከተማ አድርጌ ተጉዤ ነበር። በመጀመሪያው ጉዞየ ከአዲስ አበባ ተነስቼ ጂማ አደርኩ። በሚቀጥለው ቀን ደግሞ በሌላ የህዝብ ማመላለሻ መኪና ተሳፍሬ ጉዞየን ወደ ሚዛን ከተማ ቀጠልኩ። ከጂማ እስከ ሚዛን ያለው ጉዞ ስምንት ያህል ሰዓት ፈጀብን። ከጂማ - ሚዛን ያለው መንገድ የአስፓልት ንጣፍ ቢጀመርለትም አብዛሃኛው የመንገዱ ክፍል በፒስታ የተሸፈነ በመሆኑና ኮረኮንቻማ ስለሆነ ጉዞው በጣም አድካሚ ነበር።


 መዳረሻዬ ወዳደረኳት ዲማ ከተማ ደርሼ ቶሎ ለመመለስ ስለፈለኩ ሚዛን አውቶብስ ተራ ከወረድኩ በሗላ ቀጥታ ወደ ዲማ የሚወስደኝን መኪና ነበር ማፈላለግ የጀመረኩት ። የዕለቱን የምሳ መርሃ-ግብርም የፈፀምኩት መኪናውን ካገኘሁት በሗላ ነው ። ይህ ከላይ ሳወጋችሁ የቆየሁት ዋናው የጉዞ ትውስታዬ አይደለም። እንድሁ አነሳሴንና ዋና ዋና ያልኳቸውን  የጉዞ ትውስታዎች እስኪያጋጥሙኝ ድረስ ያለፍኩበትን በደምሳሳው ለማሳዬት እንጂ ።

Friday, August 24, 2012

የመጨረሻዋን ሰዓት በቤተ መንግስት


ጥንቅር [ሞረሽ] ምድብ[ማራኪ ገፆች]

የአዳራሹ መጋረጃዎች ስላልተከፈቱ ጭልምልም ብላል። ሀይለስላሴ ዙፋናቸው ላይ ፀጥ ብለው ተቀምጠዋል። ጊዜያቸውን ሲያጣብብ የነበረው የሰው ጋጋታ ደንብና መመሪያ ማውጣት በመቆሙ አካባቢው ጭር ብሏል ። በመጨረሻ የማያውቁት ሰው ውሳኔዎችን እየሰጠ እንደሆነ ደመደሙ ።

ራስ ካሳም በበኩላቸው ፕሮቶኮሉን ጥሰው ሌሎቹ የምክር ቤት አባላት እየተከተሏቸው አዳራሹን በርግደው ገቡ ። ንጉሰ ነገስቱ በራሶቹ መምጣት አልተገረሙም ። ምንም እንኳን መረጃ የሚያቀብላቸው ሰው ባይኖርም፣ ንጉሱ ቁጣ እንደሚቀሰቅስና ያንንም ተከትሎ የምክርቤቱ አባላት ፍርሃታቸው እንደሚጨምር ያውቃሉ።

Thursday, July 19, 2012

ያለንም እኛ የሞትንም እኛ!

የጠቅላይ ሚንስተር መለስ ዜናዊ በጠና መታምንና ከሚዲያና ከህዝብ አይን መሰዎር ሰሞኑን በህዝቡ ዉስጥ ለሚናፈሱ በርካታ ዉጅብሮች መፈጠር ምክንያት ሆኗል። ተራዉ ህዝብ ይቅርና አስተማማኝ የመረጃ ምንጮች አሉን የሚሉ ጋዜጠኞችን እንኳን ሳይቀር ለዉዥምብር የዳረገ ክስተት ነበር የሰሞኑ የጠቅላይ ሚንስተር መለስ የመታመም ዜና። የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ ጠቅላይ ሚንስተር መለስ ዜናዊ ህክምናቸዉን አጠናቀዉ ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸዉን ከታማኝ ምንጮች አረጋግጫለሁ ሲል፤ የጠቅላይ ሚንስትሩን መታመም አስመልክቶ አንዳችም ነገር ትንፍሽ ሳይል የሰንበተዉ  የሪፖርተር ጋዜጣ ባለቤት አማረ አረጋዊ በበኩሉ ጠቅላይ ሚንስተር መለስ ህክምናቸዉን አጠናቀዉ ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸዉንና በተሻለ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ፣ ነገር ግን በቅርብ ቀን ስራ እንደማይጀምሩ ዘግቧል። በሌላ በኩል የፈረንሳይ የዜና አገልግሎት የሆነዉ ኤ.ኤፍ.ፒ ጠቅላይ ሚንስተር መለስ ዜናዊ በጠና እንደታመሙና አሁንም ድረስ ቤልጀም ብራሰልስ በሚገኝ ሆስፒታል ዉስጥ በህክምና ላይ እንዳሉ በዜና ዘገባዉ አሰራጭቷል። 

 

Thursday, July 5, 2012

በኢትዮጵያ የመጀመሪያዉ/ን…

 መቸም ኢትዮጵያ ዉስጥ አድስ የተጀመረን ነገር ወይም የነበረን አገልግሎት ሲቻል  በአለም፣ ካልሆነ በአፍሪካ እነዚህ ሁለቱ ካልተሳኩ ደግሞ “በኢትዮጵያ የመጀመሪያዉ” በሚል ተቀጥላ ማስተዋወቅ በህግ ተደንግጎ የተቀጠ ግደታ እስከሚመስል ድረስ  ከግለሰብ እስከ መንግስት ተቋማት ድረስ የተለመደ ነዉ። ምናልባትም የዚህ አይነት የማስታዎቂያ ተቀጥላዎችን በብዛት በመጠቀም በአለም የመጀመሪያዎቹ ሳንሆን አንቀርም (lol አላችሁ!)።  በእዉቀቱ ስዩም “የቤተሰቦቼ ሁለተኛ ልጅ በመሆን የመጀመሪያ ነኝ”  ሲል በአሽሙር ልክልካቸዉን እንደነገራቸዉ ማለቴ ነዉ፡፡ በርግጥ ከኢትዮጵያም አልፈዉ በአለም ደረጃ ለመተግበር ቀርቶ ለማሰብ እንኳን የሚከብዱ በርካታ ስራዎችን ቀዳሚ በመሆን ያበረከቱ አሊያም ያስተዋወቁ የትየለሌ ኢትዮጵያዊያን እንዳሉ እሙን ነዉ። እነዚህን ኢትዮጵያዊያንም “የመጀመሪያዉ” በሚል የማሞካሻ የማዕረግ ተቀጽላ መጠራት ቢያንሳቸዉ እንጂ የሚበዛባቸዉ አይሆንም። ምናልባትም ዛሬ ላይ ያሉ ማስታዎቂያ ነጋሪዎችም በእዉቀቱ እንዳለዉ “የመጀመሪያዉ” የሚለዉን ተቀጽላ “እግዚያብሔርም በመጀመሪያ ሰማይና ምድርን ፈጠረ” ከሚለዉ የመጸሐፍ ቅዱስ ቃል ሳይሆን ከነዚህ ኢትዮጵያዉያን የክብር ስም ላይ ይሆናል ላፍ አድርገዉ የወሰዱት። 

Wednesday, June 27, 2012

የአፄ ሀይለ ሥላሴ እናት ማን ናቸዉ?


ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ የሚለዉ መጽሐፍ ላይም ይሁን በማንኛዉም አጋጣሚ ልጃቸዉ ቀዳማዊ ሀይለ ሥላሴ የእናታቸዉን ፎቶግራፍ አሳይተዉም ሆነ የአባት ስም ተናግረዉ አያዉቁም። ታሪክ ጸሐፊዎችም በመፍራት ሊሆን ይችላል የቀዳማዊ ሀይለ ሥላሴን የአባት ወላጆች ሲዘረዝሩ የእናታቸዉን አባት ስም ግን አይጠቅሱም። የሚገርመዉ ደግሞ  ከልጃቸዉ ህልፈተ ሕይወትም በሗላ የእናታቸዉን አባት ስም በጽሑፍ ወይም በይፋ ለመጥቀስ ብዙዎች እስካሁን አልደፈሩም። ስለኾነም በምንም ይፋ ነገር ላይ የወይዘሮ የሺ እመቤት (የአፄ ሀይለ ሥላሴ እናት) ምስል ለሕዝብ አልተናኘም። ወይዘሮ ወለተ ጊዮርጊስ ወይም ወይዘሮ ቂቶ የወይዘሮ የሺ እመቤት እናት ቁመታቸዉ አጭር ሲሆን ብስል ቀይና በጣም ዉብ የሆኑ ሴት ነበሩ። ትዉልዳቸዉም የስልጤ ጉራጌ ናቸዉ ይባላል። ከአንዲት ጉራጌ የሚወለድ ልጅ ትልቅ ንጉስ ይሆናል የሚል ትንቢት ስለነበረ የሸዋ መኳንንት ሁሉ የጉራጌ ሚስት እየፈለገ ያገባ ነበር። በተለይ የወለኔ ሴቶች ቆንጆዎች ስለነበሩ ብዙ መኳንንቶች ተረባርበዉባቸዋል። ወለኔ ወሊሶ ከተማ አጠገብ ያለ አገር ሲሆን ነዋሪዎቹ ጉራጌዎች መልካቸዉ ቀያይና ቆንጆዎች ስለሆኑ ይመረጡ ነበር። የመኳንንቶቹ አማራ ሚስቶች በቅናት ጉራጌዎቹን ሴቶች “ምርኮኞች” ይሏቸዉ ነበር። ራስ ዳርጌ ወይዘሮ ወለተ ጊዮርጊስን በይፋ ሚስትነት ሳይሆን በዕቁባትነት አስቀምጠዉ ሦስት ልጆች ወልደዋል። ይሁንና ወይዘሮ ወለተ ጊዮርጊስ ሌሎች ልጆችም ከተለያዩ ሰዎች ወልደዋል።